Thursday, June 9, 2016

በሱስ ተነክሬ

በሱስ ተነክሬ
…………………………… ውዴ !
ካንቺ ከተለየሁ ያንጊዜ ጀምሬ፤
በፍቅርሽ እግረሙቅ ቃልኪዳን ታስሬ፤
ካስቀመጥሽኝ ቦታ ዛሬም ተገትሬ፤
አለሁኝ እላለሁ በሱስ ተነክሬ፡፡
የወሰደሽ መንገድ ያመጣሻል ብዬ፤
ትንባሆ እያቦለልኩ በአፍ ባፍንጫዬ፡፡
አንቺን ባቀፈ እጄ በርጫ ታቅፌበት፤
በሳመሽ ከንፈሬ መድዓ ስቤበት፤
……………………ሲጋራ ምጌበት፡፡
በጨዋታሽ ለዛ የሳቁት ጥርሶቼ፤
በፍቅራዊ ጉርሻሽ ተሞልተው ጉንጮቼ፤
…………………………….ነበር ያኔ እላለሁ፡፡
በያዝኩት መስተዋት ጥርሴ በልዞ እያየሁ፤
ጉንጬም በታርዚና ተወጥሮ እያየሁ፡፡
በስስት መልክሽን ያዩትም ዓይኖቼ፤
በጥቅሻሽ ብዛት አልቀው ቅንድቦቼ፡፡
መብራት ባነሰበት በቦግ እ…ል…ል…..ም ሀገር
…… … …… ………ለምንስ ይዋሻል፤
ግድባቸው እስኪያልቅ ፓውዛ ሊሆናቸው
…………………………አይኔ ፈጦልሻል፡፡
………………………ቀኑ እንደሁይመሻል፤
……………………..ትናንትም ይሸሻል፡፡
ከንፈሮቼ ጠቁረው ዛሬም ያጨሳሉ፤
በሲጋራው ጢስ ውስጥ አንቺን እየሳሉ፡፡
እጆቼም ሻከሩ ፊቴም ጠቋቆረ፤
በፍቅር ቃላትሽ ገጼ ውብ ነበረ፡፡
………….ሆኖም ግን የኔ ውድ!
ማንስ እንዳሰበው እንደ እቅዱ ኖረ፤
ከመጠበቅ በቀር ቀን እየቆጠረ፡፡
…………………….እኔም ህልሜ ነበር!
ካንቺ ጋር ተጋብቶ ባንድ ጎጆ ማደር፡፡
ውዴ እንዳሰብኩት ሁሉም መች ሆነና፤
ወጥተሸ ስትቀሪ በመራሽ ጎዳና፡፡
እኔም ራሴን ትቼ እቅዴን ቀይሬ፤
ዛሬ ድረስ አለሁ በሱስ ተነክሬ፡፡
          ✍✍✍ ✍✍✍

    ቢንያም ደምሴ

1 comment: