Friday, June 10, 2016

የመስቀል ለት ማታ

‹‹‹የመስቀል ለት ማታ ›››
ከደመራው ጀርባ ከችቦው ብልጭታ፤
ከመዘምራን ጋር ዝማሬ ተጫውታ፡፡
ከተካነችው ልጅ የሚያምር ፈገግታ፤
ካፈቀርኳት ቆንጆ የመስቀል ለት ማታ፡፡
ደመራው ሲለኮስ እሳት ተቀጣጥሎ፤
በሀሳብ ከወሰደኝ ፍቅሯ ልቤን ሰቅሎ፡፡
የመስቀል ወፍ ሆና ልቤን የሰጠኋት፤
በሐበሻ ቀሚስ ዘንጣ ያየኋት፤
የመውደዴ ረሀብ የፍቅሬ ጥማት ናት፡፡
………………………..
ወረብ ስትወርብ ከበሮ ስትመታ፤
ፍቅር ካስያዘችኝ የመስቀል ለት ማታ፤
አለብኝ ቀጠሮ ላግኛት ላንድ አፍታ፤
ታዳምጠው ስሜቴን የልቤን ትርታ፡፡
በእምነት ግንባሯ ላይ መስቀል አሰርታ፤
ከሄደችው ወጣት ትናንትና ማታ፤

አለብኝ ቀጠሮ የመስቀል ለት ማታ፡፡ 
         
ቢንያም ደምሴ

   

No comments:

Post a Comment