Friday, June 10, 2016

ላምባ

‹‹‹ላምባ ›››
ለራቀችው ቆንጆ ከደስታ መከዳ፤
ህመሟ ለሆነው የሀገር ሁሉ እዳ፡፡
ዛሬ ላይ ላጣናት በእምባ እየተራጨን፤
መፈክር የያዝነው በ'ርሷ ይብቃ ብለን፡፡
…………..አደባባይ መሀል ለተሰለፍንላት፤
………….ስሟን ከስም መርጠው በፀሎት ለሚሏት፤
…………..እስቲ እናልቅስላት፡፡
እንደሷ በሲቃ ወድቆ በየጓዳ፤
ስንቱ ወገኔ ሞተ ቆይ ስንቱስ ተጎዳ፡፡
የሳቅና ደስታው ቤት እንዳይሆን ባዶ፤
ኋላ እንዳይመጣብን ሀዘናችን ከብዶ፡፡
እኔ ለርሷ ላምባ ከመስመር ወጥቼ፤
ሞቷ እንዳይደገም በእህት ወንድሞቼ፡፡
ለነበረችው ልጅ ለወንድሟ ኩታ፤
ስትሞት ከጎናችን ኩላሊቷን አጥታ፡፡
በኛ የአንድነት ክንድ ሌሎቹ ይዳኑ፤
ሞት በበጺ ይብቃ ይለፍልን ቀኑ፡፡
ችግር አልፎ ደስታ ይምጣልን መረባ፤
ግን እስከዛው ድረስ ለዛች ቆንጆ ላምባ፡፡

        
ቢንያም ደምሴ


   

No comments:

Post a Comment